Telegram Group & Telegram Channel
የእኔ ታሪክ (በ አዲስ ምዕራፍ)
ቪቪያን እንደፃፈችው........

የሰው ልጅ ታሪክ መጨረሻ የለውም። ሞት መጨረሻ ነው ብዬ እንዳልደመደም ከሚያደርጉኝ ነገሮች አንዱ ልጅ ነው። የአባቴ ታሪክ እዚህ ላይ ያበቃ ቢመስልም በእኔ እና በአሌፍ ግን ነፍስ ዘርቶ ቀጥሏል። እንዲህ ሆነ.........ወደኋላ ተመልሳ ከአባቷ ጋ ያሳለፈችውን የመጨረሻ ቀን አስታወሰች።


ያቀፏት የሕዝቅኤል እጆች ድንገት ተንሸራተው ሲወድቁ የእርሷም ልብ ላይ የሆነ ነገር ቁርጥ ብሎ ሲወድቅ ታወቃት። ለመናገር ቃላቶች አልነበሯትም አይኗ ብቻ በሚያፈሰው ውሃ ያወራል። ያ ሕይወቱን ሙሉ በመከራ ያሳለፈው ሕዝቅኤል ለዘለዓለም አልተነሳም። ከቁስሉ ሊያገግም ፣ ለብዙ አመት የተከደነው ጥርሱ ሊስቅ ፣ በእንባ ብዛት የሟሙ አይኖቹ እንደገና የተስፋ ጭላንጭል ሊያበሩ በነበረበት ቅፅበት ሕዝቅኤል ድንገት አመለጠ። ከእነሱ ከእናት እና አባቱ፣ ከእህቱ እና ከወንድሙ ጋ ተቀላቀለ....... ህይወት ፍትሃዊ አይደለችም። ያንን ሁሉ የስቃይ እና የመከራ አመታት ሲያሳልፍ ዞር ብሎ ያላየው ሞት...... ለደስታው በተቃረበ ሰዓት ግን ሊወስደው አሰፈሰፈ።


ማቲያስ የተደወለለትን ስልክ አናግሮ ከጨረሰ በኋላ አንድ ጋዜጣ እያነበበ የነበረ ሰው አጠገብ ሄዶ ተቀመጠ። የሰውዬውን ሁኔታ ከላይ እስከታች አጤነው....የሚያውቀው መስሎ ተሰማው ግን የት እንደሆነ ማስታወስ አልቻለም ለዛም ሊያናግረው ፈልጎ ጉሮሮውን ጠራረገ። እንዴት ዋሉ አባ.....? ሰውየው ጋዜጣቸውን ዝቅ አድርገው ወደጠራቸው ሰው ዞር አሉና ፈገግ አሉ። ምኔን አይተህ ነው አባ ያልከኝ ልጄ .......ፂምወትን አለ ቀለል ያሉ ሰው እንደሆኑ ከንግግራቸው ተረድቶ......ቀጠል አድርጎም እርሶስ ምኔን አይተው ነው ልጄ ያሉኝ አለ ጨዋታ ለመፍጠር ያክል.......እሳቸውም ወጣትነትን ብለው ፈገግ አሉ። ማቲያስ እባላለሁ አለ እጁን ለሰላምታ እየዘረጋላቸው፤ ሰውየው ድንግጥ ብለው ማቲያስ አሉ የተዘረጋላቸውን እጅ እየጨበጡ። አወ የእርሶስ አለ ማቲያስ የፊታቸውን መቀየር እያጤነ። የእኔን ስም ነበር ማቲያስ ያልኩህ ማቲያስ እባላለሁ ..........የስማችን መመሳሰል ገርሞኝ ነውኮ መደንገጤ።


ወጣቱ ማቲያስ ወዲያው የሜሮን የቀድሞ ፍቅረኛ አእምሮው ላይ ብልጭ አለ። ጋሽ ሕዝቅኤል ጓደኛወት ነው? አብርሃምም?.....ሽማግሌው ደነገጠ ማነህ አንተ?..............መጀመሪያ ጥያቄዬን ይመልሱልኛ.... አወ ማን ነህ?......የሜሮን ልጅ.........በእድሜ ብዛት የማያረጀወሰ የሽማግሌው ማትያስ ፍቅር ስሟን ሲሰማ እንደገና አገረሸ። ወጣቱን አስተዋለው እውነትም እሷን ይመስላል ..........እኔኮ አመጣጤ ሕዝቅኤል መታመሙን ሰምቼ ነበር......አለ አሁንም ድንጋጤው እንደወረረው። ና ወደውስጥ ጋሽ ሕዝቅኤልንም እየው እማዬም አለች.........ተያይዘው ወደውስጥ ገቡ።.......ሲገቡ ግን የሕዝቅኤል አይኖች ከሚወደው ጓደኛው ከማትያስም በቅፅበታት ቀድመው ተከድነዋል።


ሆስፒታሉ ሌላ ድባብ ሞልቶታል ቃል የሞላው ቃል አልባ እንባ ከየ አቅጣጫው ይፈሳል ማቲያስ በቁሙ ራደ። ሀዘን ሀዘን ብቻ ተነበበ። ሁሉም የምሬት እንባውን ያነባል......የአሌፍ ግን ቃልም አለው። ለዚህ ነው እንዳውቅህ ያደረግከው? ትተኸኝ ለመሄድ...አባ ለምን? እስከዛሬ ትናፍቀኝ አልነበረ? ስታገኘኝ ጥለኸኝ ለመሔድ ነበር?


ግን ሆነ ሕዝቅኤል ላይመለስ አይኖቹ ተከደኑ። የሚወዱትም ነፍሶች ላይጠገኑ ተሰበሩ። ስርዓተ ቀብሩም ራቢያም ራሷ በተገኘችበት ተፈፀመ።ራቢያ ለዚህ ሁሉ አመታት አፍና የያዘችውን የስቃይ እንባ በመቃብሩ ላይ ዘረገፈችው አልቅሳ አልቅሳ አልጠገበችም አትጠግብምም። አለመኖሩን ሳታይ አምና የነበረችው ራቢያ አይታ ስታረጋግጥ ግን ለመቀበል አልቻለችም አቃታት።


ኤልሳ ልትናገር ይቅርና መቆም አቅቷት ለቀብሩም በሰወች ተደግፋ ነበር የመጣችው። የመጨረሻ ቃሏ " ላልድን ሰበርከኝ አይደል?" የሚል ነበር ከዛ ቃል በኋላ ከ አፏ የወጣ አንድም ቃል የለም። የእሷም አንደበት ከ ህዝቅኤል ጋር ተቀበረ።


ቪቪያን ውስጧ ነው የሚያወራው አይኗ ደግሞ በእንባ ቃላቶቹን ያወጣል። ብቻ ግን ስትታይ ከማዘን አልፎ ሕመሟ ይጋባል ።
ጓደኛው ማቲያስ ቪቪያንን አይቷት ውስጧን አነበበው። እንደ ሕዝቅኤልም ሊጠብቃት ለራሱ ቃል ገባ።
ሁሉንም ሰው በአንድ ላይ የሰበረ ቀን.....

ይቀጥላል ........

@nibab_lehiwot
@nibab_lehiwot
@nibab_lehiwot



tg-me.com/nibab_lehiwot/196
Create:
Last Update:

የእኔ ታሪክ (በ አዲስ ምዕራፍ)
ቪቪያን እንደፃፈችው........

የሰው ልጅ ታሪክ መጨረሻ የለውም። ሞት መጨረሻ ነው ብዬ እንዳልደመደም ከሚያደርጉኝ ነገሮች አንዱ ልጅ ነው። የአባቴ ታሪክ እዚህ ላይ ያበቃ ቢመስልም በእኔ እና በአሌፍ ግን ነፍስ ዘርቶ ቀጥሏል። እንዲህ ሆነ.........ወደኋላ ተመልሳ ከአባቷ ጋ ያሳለፈችውን የመጨረሻ ቀን አስታወሰች።


ያቀፏት የሕዝቅኤል እጆች ድንገት ተንሸራተው ሲወድቁ የእርሷም ልብ ላይ የሆነ ነገር ቁርጥ ብሎ ሲወድቅ ታወቃት። ለመናገር ቃላቶች አልነበሯትም አይኗ ብቻ በሚያፈሰው ውሃ ያወራል። ያ ሕይወቱን ሙሉ በመከራ ያሳለፈው ሕዝቅኤል ለዘለዓለም አልተነሳም። ከቁስሉ ሊያገግም ፣ ለብዙ አመት የተከደነው ጥርሱ ሊስቅ ፣ በእንባ ብዛት የሟሙ አይኖቹ እንደገና የተስፋ ጭላንጭል ሊያበሩ በነበረበት ቅፅበት ሕዝቅኤል ድንገት አመለጠ። ከእነሱ ከእናት እና አባቱ፣ ከእህቱ እና ከወንድሙ ጋ ተቀላቀለ....... ህይወት ፍትሃዊ አይደለችም። ያንን ሁሉ የስቃይ እና የመከራ አመታት ሲያሳልፍ ዞር ብሎ ያላየው ሞት...... ለደስታው በተቃረበ ሰዓት ግን ሊወስደው አሰፈሰፈ።


ማቲያስ የተደወለለትን ስልክ አናግሮ ከጨረሰ በኋላ አንድ ጋዜጣ እያነበበ የነበረ ሰው አጠገብ ሄዶ ተቀመጠ። የሰውዬውን ሁኔታ ከላይ እስከታች አጤነው....የሚያውቀው መስሎ ተሰማው ግን የት እንደሆነ ማስታወስ አልቻለም ለዛም ሊያናግረው ፈልጎ ጉሮሮውን ጠራረገ። እንዴት ዋሉ አባ.....? ሰውየው ጋዜጣቸውን ዝቅ አድርገው ወደጠራቸው ሰው ዞር አሉና ፈገግ አሉ። ምኔን አይተህ ነው አባ ያልከኝ ልጄ .......ፂምወትን አለ ቀለል ያሉ ሰው እንደሆኑ ከንግግራቸው ተረድቶ......ቀጠል አድርጎም እርሶስ ምኔን አይተው ነው ልጄ ያሉኝ አለ ጨዋታ ለመፍጠር ያክል.......እሳቸውም ወጣትነትን ብለው ፈገግ አሉ። ማቲያስ እባላለሁ አለ እጁን ለሰላምታ እየዘረጋላቸው፤ ሰውየው ድንግጥ ብለው ማቲያስ አሉ የተዘረጋላቸውን እጅ እየጨበጡ። አወ የእርሶስ አለ ማቲያስ የፊታቸውን መቀየር እያጤነ። የእኔን ስም ነበር ማቲያስ ያልኩህ ማቲያስ እባላለሁ ..........የስማችን መመሳሰል ገርሞኝ ነውኮ መደንገጤ።


ወጣቱ ማቲያስ ወዲያው የሜሮን የቀድሞ ፍቅረኛ አእምሮው ላይ ብልጭ አለ። ጋሽ ሕዝቅኤል ጓደኛወት ነው? አብርሃምም?.....ሽማግሌው ደነገጠ ማነህ አንተ?..............መጀመሪያ ጥያቄዬን ይመልሱልኛ.... አወ ማን ነህ?......የሜሮን ልጅ.........በእድሜ ብዛት የማያረጀወሰ የሽማግሌው ማትያስ ፍቅር ስሟን ሲሰማ እንደገና አገረሸ። ወጣቱን አስተዋለው እውነትም እሷን ይመስላል ..........እኔኮ አመጣጤ ሕዝቅኤል መታመሙን ሰምቼ ነበር......አለ አሁንም ድንጋጤው እንደወረረው። ና ወደውስጥ ጋሽ ሕዝቅኤልንም እየው እማዬም አለች.........ተያይዘው ወደውስጥ ገቡ።.......ሲገቡ ግን የሕዝቅኤል አይኖች ከሚወደው ጓደኛው ከማትያስም በቅፅበታት ቀድመው ተከድነዋል።


ሆስፒታሉ ሌላ ድባብ ሞልቶታል ቃል የሞላው ቃል አልባ እንባ ከየ አቅጣጫው ይፈሳል ማቲያስ በቁሙ ራደ። ሀዘን ሀዘን ብቻ ተነበበ። ሁሉም የምሬት እንባውን ያነባል......የአሌፍ ግን ቃልም አለው። ለዚህ ነው እንዳውቅህ ያደረግከው? ትተኸኝ ለመሄድ...አባ ለምን? እስከዛሬ ትናፍቀኝ አልነበረ? ስታገኘኝ ጥለኸኝ ለመሔድ ነበር?


ግን ሆነ ሕዝቅኤል ላይመለስ አይኖቹ ተከደኑ። የሚወዱትም ነፍሶች ላይጠገኑ ተሰበሩ። ስርዓተ ቀብሩም ራቢያም ራሷ በተገኘችበት ተፈፀመ።ራቢያ ለዚህ ሁሉ አመታት አፍና የያዘችውን የስቃይ እንባ በመቃብሩ ላይ ዘረገፈችው አልቅሳ አልቅሳ አልጠገበችም አትጠግብምም። አለመኖሩን ሳታይ አምና የነበረችው ራቢያ አይታ ስታረጋግጥ ግን ለመቀበል አልቻለችም አቃታት።


ኤልሳ ልትናገር ይቅርና መቆም አቅቷት ለቀብሩም በሰወች ተደግፋ ነበር የመጣችው። የመጨረሻ ቃሏ " ላልድን ሰበርከኝ አይደል?" የሚል ነበር ከዛ ቃል በኋላ ከ አፏ የወጣ አንድም ቃል የለም። የእሷም አንደበት ከ ህዝቅኤል ጋር ተቀበረ።


ቪቪያን ውስጧ ነው የሚያወራው አይኗ ደግሞ በእንባ ቃላቶቹን ያወጣል። ብቻ ግን ስትታይ ከማዘን አልፎ ሕመሟ ይጋባል ።
ጓደኛው ማቲያስ ቪቪያንን አይቷት ውስጧን አነበበው። እንደ ሕዝቅኤልም ሊጠብቃት ለራሱ ቃል ገባ።
ሁሉንም ሰው በአንድ ላይ የሰበረ ቀን.....

ይቀጥላል ........

@nibab_lehiwot
@nibab_lehiwot
@nibab_lehiwot

BY ሕይወትን - በገፅ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/nibab_lehiwot/196

View MORE
Open in Telegram


ሕይወትን በገፅ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram announces Anonymous Admins

The cloud-based messaging platform is also adding Anonymous Group Admins feature. As per Telegram, this feature is being introduced for safer protests. As per the Telegram blog post, users can “Toggle Remain Anonymous in Admin rights to enable Batman mode. The anonymized admin will be hidden in the list of group members, and their messages in the chat will be signed with the group name, similar to channel posts.”

If riding a bucking bronco is your idea of fun, you’re going to love what the stock market has in store. Consider this past week’s ride a preview.The week’s action didn’t look like much, if you didn’t know better. The Dow Jones Industrial Average rose 213.12 points or 0.6%, while the S&P 500 advanced 0.5%, and the Nasdaq Composite ended little changed.

ሕይወትን በገፅ from tw


Telegram ሕይወትን - በገፅ
FROM USA